
የሙዚቃ
ትምህርት ቤት በአዲስ አበባ የተከፈተው በ1887 ዓ.ም. ነው፡፡ምኒሊክ ከሩሲያ የሙዚቃ አስተማሪ አስመጥተው ትምህርት ቤቱን
በከፈቱበት ጊዜ ከመምህሩ ጋር 40 የተለያዩ የሙዚቃ መሳሪያዎች መጥተው ነበር፡፡አሁን ያለው አንጋፋው የያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት
ተመርቆ የተከፈተው ሰኔ 30 ቀን 1962 ዓ.ም. ነበር፡፡አይ እምዬ ምኒሊክ!
በኢትዮጵያ
የሙዚቃ ታሪክ ( Recording History ) በሸክላ
የተቀረፁት የመጀመሪያ ስራዎች የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ዜማዎች ሲሆኑ ዘመኑም በአጤ ምኒሊክ ዘመነ መንግስት ነበር፡፡
ተሰማ እሸቴ የተላኩበትን የመካኒክነት ትምህርት አጠናቀው አጥጋቢ ውጤት ከማምጣታቸውም
በላይ የመጀመሪያውን የአማርኛ ዜማ ሸክላ እዚያው በጀርመን ሀገር አስቀረፁ፡፡በጀርመን ቆይታቸው ወቅት የጀርመን የሙዚቃ ድርጅት ጠይቋቸው የኢትዮጵያ መዲናና ዘለሰኛ ዜማዎችን በ17 አይነት ስልት
ተጫወቱ፡፡

በ1925-26 አካባቢ ዓ.ም. አካባቢ የእነ ፈረደ ጎላ፤ንጋቷ ከልካይ እና ተሻለ መንግስቱ የዜማ ሸክላዎች
ብቅ እካሉ ድረስ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ሸክላዎች ከ20 አመታት በላይ አቅም ባላቸው ቤተሰቦች ዘንድ በብቸኝነት በግራማፎን ሲደመጡ
ቆይተዋል፡፡
No comments:
Post a Comment