Wednesday, July 31, 2013

እስትንፋሱን ለማቆየት የወገኖቹን እርዳታ የሚጠብቀው ታዳጊ- ሙሉ ብርሃን-ቪዲዮውን ይመልከቱ



           

ሙሉ ብርሃን ይባላል 16 ዓመቱ ነው ፡፡አዲግራት ሆስፒታል መኖር ከጀመረ 3 ዓመት በላይ ሆኖታል፡፡ በመተንፈሻ አካሉ ላይ በደረሰበት ጉዳት ምክንያት በአፍንጫው መተንፈስ አይችልም፡፡ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በተደረገለት የቀዶ ጥገና በአንገቱ ላይ በተሰራለት ሰው ሰራሽ መሳሪያ በመተገዝ ነው የሚተነፍሰው፡፡
በሆስፒታሉ የሚኖረው የሚተነፍስበት መሳሪያ ለማፅዳት የሚያግዘው መሳሪያ በሆስፒታሉ ስለሚገኝ ነው ፡፡
ሐኪሞች እንደነገሩት የሚረዳው ቢያገኝ እና ውጭ ሃገር መሄድ ቢችል ዳግም በአፍንጫው መተንፈስ ይችላል፡፡ ህክምናው የሚጠይቀውን ወጪ ቤተሰቦቹ ለመሸፈን አቅም የላቸውም፡፡ አባቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል አናቱ ደግሞ አቅመ ደካማ ናቸው ፡፡ የቤተሰቡ ሁለተኛ ልጅ የሆነውን ሙሉብርሃንን ለመተደግ እጆን ይዘርጉለት ፡፡ሙሉብረሃንን ለመርዳት በቬዲዮ ላይ ባሉት ስልክ ቁጥሮች ያገኙታል፡፡

No comments:

Post a Comment